የመንግሥት ሃይማኖት
ከWikipedia
የመንግሥት ሃይማኖት በአንድ መንግሥት ዘንድ የተመሠረተ ሃይማኖት ወይም ይፋዊ እምነት ነው። ይህ ሲባል ግን የተመሠረተው ሃይማኖት መሪዎች የመንግሥቱ መሪዎች አይደሉም፤ እንደዚህ ከሆነ ግን ያው መንግስት «Theocracy» ይባል ነበር። 'የተመሠረተው ሃይማኖት' ማለት በመንግሥት የተደገፈው እምነት ወይም ትምህርት የሚመለከት ነው።
ይዞታ |
[ለማስተካከል] አይነቶች
መንግሥት ሃይማኖቱን እስከ ምን ደረጃ ድረስ እንደሚደግፈው በየአገሩ ይለያያል። ከቃል ድገፋ ብቻ እስከ ገንዘባዊ እርዳታ ድረስ ሊሆን ይችላል። በአንዳንድ አገር ውስጥ የሌሎቹ ሃይማኖቶች ተከታዮች ነጻነት ቢያገኙም በሌላ አገር በኩል ግን ሌላ ሃይማኖት ሁሉ ይከለከላል። ወይም ተከታዮቹ ይሳድዳሉ።
በአውሮፓ ውስጥ የካቶሊክና የፕሮቴስታንት (ወይም ጸረ ማርያም የተባሉት) አብያተ ክርስትያናት በ16ኛ ክፍለ ዘመን ሲወዳደሩና ሲተጋገሉ፤ መንግሥታት የመሪዎቻቸውን ምርጫ ተከተሉ፤ ይህም መርኅ በአውግስቡርግ ውል (1547 ዓ.ም.) ጸደቀ። የእንግሊዝ ንጉሥ በ1525 ዓ.ም. የፕሮቴስታንት እምነት ስለ አጸደቀ፤ በፓፓ ፈንታ የእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን ላይኛ መሪ እሱ ሆነ። በስኮትላንድ ግን በመቃወም የስኮትላንድ ቤተ ክርስቲያን ይፋዊ ሆነ።
አንዳንዴ፣ አንድ አገር ወይም ክፍለሀገር ልዩ ልዩ ሃይማኖቶች በገንዘብ ይደግፋል። ለምሳሌ በፈረንሳይ ውስጥ በአልሳስ-ሞዘል ጠቅላይ-ግዛት እንዲሁም በጀርመን አገር እንዲህ ይደረጋል።
በአንዳንድ ኮሙኒስት አገር በተለይ በቻይና ሕዝባዊ ሪፐብሊክ፤ መንግስት አንዳንድ ሃይማኖት ድርጅት ብቻ ይፈቀዳልና ሌሎቹ አይፈቀዱም። እንደነዚህ ባሉት አገሮች የተመረጠው ትምህርት ወይም እምነት የማርክስ ወይም የማው ጸ-ቱንግ ጽሑፎች ይሆናል።
[ለማስተካከል] ከመመሠረት መነቀል (Disestablishment)
ከመመሠረት መነቀል (Disestablishment) ማለት አንድ ሃይማኖት ወይም ቤተ ክርስቲያን የመንግስት አካል ከመሆን የሚቋረጥበት ሂደት ነው። ለምሳሌ በእንግሊዝ አገር በመጨረሻ 19ኛ ክፍለ ዘመን እንዲህ ለማድረግ የታገለ እንቅስቃሴ ቢኖርም አልተከናወነምና መቸም አልሆነም። በአይርላንድ ግን የአይርላንድ ቤተ ክርስቲያን በ1863 ዓ.ም. ከመመሠረት ተነቀለ። በ1912 ዓ.ም. ደግሞ በዌልስ ውስጥ የእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን ከመመሠረት ተነቀለ።
በአሜሪካ ሕገ መንግሥት (1ኛ የሕግ መለወጫ፣ 1783 ዓ.ም.) መሠረት ምንም ሃይማኖት እንዳይመሠረት በግልጽ ይከለከላል። ከዚህም ጋር መንግስት በሃይማኖቶች ጉዳይ ጥልቅ ከማለት ይከለከላል። ሆኖም የተወሰነ ክፍላገር መንግሥት የተመሠረተ ሃይማኖት ከመኖር አይከለክልም። ለምሳሌ ኮነቲከት እስከ 1810 ዓ.ም. ድረስ ይፋዊ ቤተ ክርስቲያን ነበረው፤ ማሳቹሰትስም እስከ 1825 ዓ.ም. ድረስ ይፋዊ ቤተ ክርስቲያን ነበረው።
ዛሬ የአሜሪካ ክፍላገሮች ሁሉ ለኗሪዎቻቸው የሃይማኖት ነጻነት ያረጋግጣሉ። ከነዚህም መካከል 8ቱ እነሱም አርካንሳው፣ ሜሪላንድ፣ ማሳቹሰትስ፣ ስሜን ካሮላይና፣ ፔንስልቬኒያ፣ ደቡብ ካሮላይና፣ ተነሲና ቴክሳስ፤ እምነተ ቢስ ሰው ከመሾም ቢከለክሉም ይህ አይነት ሕግ ግን አሁን (ከ1953 ዓ.ም. ጀምሮ) ተግባራዊ ሆኖ አይቆጠረም።
[ለማስተካከል] ክርስቲያን አገሮች
የሚከተሉት መንግስታት የክርስትና ቤተ ክርስቲያን ዓይነት በየአይነቱ መሠርተዋል።
[ለማስተካከል] ሮማ ካቶሊክ
እነዚህ አገራት ወይም ክፍላገራት የሮማ ካቶሊክ ሃይማኖት በይፋ አላችው።
- አንዶራ
- አርጀንቲና
- ቦሊቪያ
- ኮስታ ሪካ
- ኤል ሳልቫዶር
- ሊክተንስታይን
- ማልታ
- ሞናኮ
- በስዊስ አገር እነዚህ ክፍላገራት፦
- አፐንጸል ኢነሮደን
- አርጋው*
- ባዘልቤት*
- በርን*
- ግላሩስ**
- ግራውቢውንደን**
- ኒድቫልደን
- ሽቪውጽ**
- ቶርጋው**
- ኡሪ**
- ቫቲካን ከተማ
- *(ከተሐድሶ እና ከጥንታዊ ካቶሊክ ጋር)
- **(ከተሐድሶ ጋር)
[ለማስተካከል] ምስራቅ ኦርቶዶክስ
እነዚህ መንግሥታት የምስራቅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አይነት በይፋ አሏቸው።
- *(ከሉተራን ጋር)
[ለማስተካከል] ሉተራን
እነዚህ መንግሥታት የሉተራን ቤተክርስቲያን አይነት በይፋ አላቸው።
- ዴንማርክ (የዴንማርክ ቤተክርስቲያን)
- አይስላንድ (የአይስላንድ ቤተክርስቲያን)
- ኖርዌ (የኖርዌ ቤተክርስቲያን)
- ፊንላንድ (የፊንላንድ ወንጌላዊ ሉተራን ቤተክርስቲያን)*
- *(ከምሥራቅ ኦርቶዶክስ ጋር)
[ለማስተካከል] አንግሊካን
ይህ መንግሥት የአንግሊካን ቤተክርስቲያን አይነት በይፋ አለው።
- እንግሊዝ (የእንግሊዝ ቤተክርስቲያን)
[ለማስተካከል] ተሐድሶ (ሪፎርምድ)
እነዚህ መንግሥታት የተሐድሶ ቤተክርስቲያን አይነት በይፋ አላቸው።
- በስዊስ አገር እነዚህ ክፍላገራት (የስዊስ ተሐድሶ ቤተክርስቲያን) ፦
- አርጋው*
- ባዘልቤት*
- በርን*
- ግላሩስ**
- ግራውቢውንደን**
- ሽቪውጽ**
- ቶርጋው**
- ኡሪ**
- ጹሪክ
- ስኮትላንድ - የስኮትላንድ ቤተክርስቲያን 'አገራዊ ሃይማኖት' ሲሆን ከመንግሥት ሙሉ ነጻነት አለው።
- *(ከሮማ ካቶሊክ እና ከጥንታዊ ካቶሊክ ጋር)
- **(ከሮማ ካቶሊክ ጋር)
[ለማስተካከል] ጥንታዊ ካቶሊክ
እነዚህ መንግሥታት 'ጥንታዊ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን' የተባለው አይነት በይፋ አላቸው።
- በስዊስ አገር እነዚህ ክፍላገራት ('የስዊስ ክርስቲያን ካቶሊክ ቤተክርስቲያን') ፦
- አርጋው
- ባዘልቤት
- በርን
(በነዚህም 3 ውስጥ የሮማ ካቶሊክና የተሐድሶ አይነቶች አብረው ይፋዊ ናቸው)
[ለማስተካከል] የእስላም አገሮች
የሚከተሉት መንግስታት የእስልምና ዓይነት በይፋ መሠርተዋል።
- አፍጋኒስታን
- አልጄሪያ (ሱኒ እስልምና)
- ባሕሬን
- ባንግላዴሽ
- ብሩኔይ
- ኮሞሮስ (ሱኒ)
- ግብጽ
- ፋርስ (ሺዓ እስልምና)
- ኢራቅ
- ዮርዳኖስ
- ኩዌይት
- ሊብያ
- ማላይዢያ (ሱኒ)
- ማልዲቭስ ደሴቶች (ሱኒ)
- ሞሪታኒያ
- ሞሮኮ
- ኦማን
- ፓኪስታን (ሱኒ)
- ቃጣር
- ምዕራባዊ ሣህራ
- ሳዑዲ አረቢያ (ሱኒ)
- ሶማሊያ (ሱኒ)
- ሶማሊላንድ
- ቱኒዚያ
- የተባበሩት አረብ ኤሚራቶች
- የመን
- ዮርዳኖስ (ሱኒ)
[ለማስተካከል] የቡዲስት አገሮች
የሚከተሉት መንግስታት የቡዳ ሃይማኖት ዓይነት በይፋ መሠርተዋል።
- ቡታን ('ድሩክፓ ካግዩ' ቲቤታዊ አይነት)
- ካምቦዲያ ('ጤራቫዳ' አይነት)
- በሩስያ ውስጥ የሆነ ክፍላገር፦
- ካልሙኪያ (ቲቤታዊ አይነት)
- ስሪ ላንካ (ጤራቫዳ አይነት)
- ታይላንድ (ጤራቫዳ አይነት)
- ምየንማ
[ለማስተካከል] ሕንዱ አገራት
ከአገራት ኔፓል ብቻ የሕንዱ ሃይማኖትን በኦፊሴል ይዞ ነበር። በቅርብ ጊዜ ግን፣ በአመጻዎች ችግር ምክንያት ይህ ሁኔታ ተለውጦ እምነቱ ከመመሰረት ተነቀለ።
[ለማስተካከል] አይሁድና
በእስራኤል ሕገጋት መሠረት አገሩ 'የአይሁድ አገር' ይባላል። ይሁንና 'አይሁድ' የሚለው ቃል ሃይማኖት ብቻ ሳይሆን አንድ ዘር ወይም ወገን ማለት ደግሞ ሊሆን ይችላል። ስለዚህ አይሁድና ምን ማለት እንደሚሆን ለአገሩ ክርክር ሆኗል። አሁን እስራኤል አንዳንድ ተቋም በተለይም የኦርቶዶክስ አይሁድ ተቅዋማት ይደግፋል፤ ከዚህም በላይ የኦርቶዶክስ አይሁድ፣ የእስላም፤ የክርስቲያንና የድሩዝ ችሎቶች ይፈቅዳል።
[ለማስተካከል] በጥንት
[ለማስተካከል] ሱመር
በጥንት ሱመር መንግሥታት የመንግስት ሃይማኖት ጽንሰ ሀሣብ ይታወቅ ነበር። እያንዳንዱ ከተማ-አገር ወይም ሕዝብ የራሱን አማልክት ወይም ጣኦት ይኖሩት ነበር። የድሮ ሱመር አለቆች ብዙ ግዜ ለከተማቸው አምላክ ቄሶች ደግሞ ነበሩ።
[ለማስተካከል] ግሪክ
ሰዎቹ በብዙ አማልክት ቢያምኑም እያንዳንዱ ጥንታዊ ግሪክ ከተማ የገዛ ዐቃቤ አምላኩ ነበረው። እንዲሁም የአቴና አምላክ አቴና ነበረች፤ የስፓርታም አርቴሚስ፣ የዴሎስ አፖሎ፣ የኦሊምፒያ ዜውስ ነበሩ።
[ለማስተካከል] ቻይና
በቻይና የሃን ሥርወ መንግሥት (214 ክ.በ. - 212 ዓ.ም.) የኮንፉክዩስ (ኮንግፉጸ) ሃይማኖት በይፋ ተከተለ። ወደ ማዕረግ ለመሾም ዕጩዎቹ በዚህ እምነት መጻሕፍት ይፈተኑ ነበር። ይህ ሃይማኖት እስከ 573 ዓ.ም. ድረስ ይፋዊ ሆኖ ቀጠለ። ያንጊዜ የቻይና መንግስት ሃይማኖት የቡዳ ሃይማኖት ሆነ። ዳሩ ግን በ10ኛ መቶ ዘመን ውስጥ መንግሥቱ ወደ ኮንፉክዩስ ሃይማኖት ተመለሰ።
[ለማስተካከል] የሮማ ሃይማኖት
በሮማ መንግሥት ላይኛ ቄስ የተባለው ቄሳር ወይም ንጉሡ ነበረ። ብዙ ግዜ ንጉሡ በትእቢቱ ብዛት እኔ አምላክ ነኝ በግልጽ ያዋጅ ነበር። በአንዳንድ ወቅት ደግሞ ለንጉሡ ካልጸለዩ ይሙት በቃ በሕዝብ ላይ ደረሰባቸው። በዚህ ዘመን ብዙ ክርስቲያኖችና አይሁዶች ለሮማ ንጉስ አንጸለይም ብለው ተገደሉ።
በ303 ዓ.ም. ንጉሡ ጋሌሪዎስ አልጋ ላይ ወድቆ ትንሽ ሊያርፍ ሲል በመንግሥቱ ግዛት ውስጥ ላሉት ክርስቲያኖች ሁሉ ይቅርታ ሰጠ። ከዚህ በፊት የክርስትናን ሃይማኖት ለማጥፋት በሙሉ ሞክሮ ነበር። ከዚያ ሁለት የጋርዮሽ ቄሣሮች 1ኛ ቆስጠንጢኖስ እና ሊቂኒዎስ በ305 ዓ.ም. የሚላኖ አዋጅን አወጡ። ይህ ህግ ለሰው ሁሉ የሃይማኖት ነጻነት በማረጋገጥ የክርስቲያኖች መሬት ያለ ገደብ እንዲመልስላቸው የሚያዝዝ ነበር።
በ317 ዓ.ም. ቆስጠንጢኖስ የኒቂያ ጉባኤ ጠሩ። ቢባልም ለብዙ አመታት ከዚህ በኋላ በጥምቀት እንዳልገቡ መገንዘብ ይረዳል። አሁን ክርስትና በሮማ ውስጥ በይፋ የመንግሥት ሃይማኖት ባይሆን በብዙዎች ሕዝብ በግልጽ ይከተል ጀመር። በዚህ ዘመን አካባቢ ግን የሮማ መንግሥት ጎረቤቶች የነበሩት የአክሱም መንግሥትና አርሜኒያ ከነገስታታቸው ጥምቀት አንስቶ በይፋ ወደ ክርስትና ገብተው ነበር።
ለጥቂት ግዜ ከ353 እስከ 355 ዓ.ም. ድረስ የሮማ ንጉሥ ዩሊያኖስ ከሐዲ መንግሥቱን ወደ ድሮ አረመኔ እምነት መለሠው። ተከታዩ ግን ክርስቲያን በመሆኑ አገሩን ወደ ክርስትና ፕሮግራም መለሰ።
በመጨረቫ በ372 ዓ.ም. የካቶሊክ ቤተክርስቲያን በንጉሡ 1ኛ ቴዎዶስዮስ አዋጅ መሠረት የሮማ መንግስት ሃይማኖት በይፋ ተደረገ።
[ለማስተካከል] ፋርስ
የሳሳኒድ መንግሥት (218-643 ዓ.ም.) ይፋዊ ሃይማኖት የዛርጡሽ ሃይማኖት ነበር።
[ለማስተካከል] በአውሮፓ ውስጥ ያሉት መንግሥታት ሃይማኖቶች ወይም ቀድሞ የነበሯቸው ሃይማኖቶች
ሀገር | ሃይማኖት | አይነት | ከመመሰረት የተነቀለበት አመተ ምኅረት |
---|---|---|---|
አልባኒያ | ከነጻነት ጀምሮ የለም | ||
አንዶራ | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | አልተነቀለም |
አንሃልት (ጀርመን) | የአንሃልት ወንጌላዊ ቤተክርስቲያን | ሉተራን | 1910 |
አርሜኒያ | የአርሜንያ ሃዋርያዊ ቤተክርስቲያን | ተዋሕዶ | 1913 |
ኦስትሪያ | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | 1910 |
ባደን (ጀርመን) | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን እና የባደን ወንጌላዊ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክና ሉተራን | 1910 |
ባየርን (ጀርመን) | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | 1910 |
ብሩንዝቪግ-ሊውነቡርግ (ጀርመን) | የብሩንዝቪግ ወንጌላዊ ሉተራን ቤተክርስቲያን | ሉተራን | 1910 |
ቡልጋሪያ | የቡልጋርያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን | ምሥራቅ ኦርቶዶክስ | 1938 |
ቆጵሮስ | የቆጵሮስ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን | ምሥራቅ ኦርቶዶክስ | አልተነቀለም |
ቼኮስሎቫኪያ | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | 1912 |
ዴንማርክ | የዴንማርክ ቤተክርስቲያን | ሉተራን | አልተነቀለም |
እንግሊዝ | የእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን | አንግሊካን | አልተነቀለም |
ኤስቶኒያ | የኤስቶኒያ ሐዋርያዊ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን | ምሥራቅ ኦርቶዶክስ | 1932 |
ፊንላንድ | የፊንላንድ ወንጌላዊ ሉተራን ቤተክርስቲያን | ሉተራን | 1911 |
ፈረንሳይ | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | 1897 |
ጂዮርጂያ | የጂዮርጂያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን | ምሥራቅ ኦርቶዶክስ | 1913 |
ግሪክ | የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን | ምሥራቅ ኦርቶዶክስ | አልተነቀለም |
ሄሰ (ጀርመን) | የሄሰ እና የናሶ ወንጌላዊ ቤተክርስቲያን | ሉተራን | 1910 |
ሀንጋሪ | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | 1840 |
አይስላንድ | የአይስላንድ ቤተክርስቲያን | ሉተራን | አልተነቀለም |
አይርላንድ | የአይርላንድ ቤተክርስቲያን | አንግሊካን | 1863 |
አየርላንድ ሪፑብሊክ | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | 1965 |
ጣልያን | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | 1976 |
ሊክተንስታይን | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | አልተነቀለም |
ሊፐ (ጀርመን) | የሊፐ ቤተክርስቲያን | ተሐድሶ | 1910 |
ሊትዌኒያ | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | 1932 |
ሊውበክ (ጀርመን) | ስሜን እልባዊ ወንጌላዊ ቤተክርስቲያን | ሉተራን | 1910 |
ሉክሳምቡርግ | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | አልተነቀለም |
ማልታ | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | አልተነቀለም |
ሜክለንቡርግ (ጀርመን) | የሜክለንቡርግ ወንጌላዊ ቤተክርስቲያን | ሉተራን | 1910 |
ሞናኮ | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | አልተነቀለም |
ሆላንድ | የሆላንድ ተሐድሶ ቤተክርስቲያን | ተሐድሶ | 1787 |
ኖርዌ | የኖርዌ ቤተክርስቲያን | ሉተራን | አልተነቀለም |
ኦልደንቡርግ (ጀርመን) | የኦልደንቡርግ ወንጌላዊ ሉተራን ቤተክርስቲያን | ሉተራን | 1910 |
ፖላንድ | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | 1931 |
ፖርቱጋል | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | 1902 |
ፕሩሲያ (ጀርመን) | 13 የጀርመን ወንጌላዊ አብያተ ክርስትያናት | ሉተራን | 1910 |
ሮማኒያ | የሮማኒያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን | ምሥራቅ ኦርቶዶክስ | 1939 |
ሩሲያ | የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን | ምሥራቅ ኦርቶዶክስ | 1909 |
ጦሪንገን (ጀርመን) | የጦሪንገን ወንጌላዊ ቤተክርስቲያን | ሉተራን | 1910 |
ሳክሰን (ጀርመን) | የሳክሰን ወንጌላዊ ቤተክርስቲያን | ሉተራን | 1910 |
ሻውምቡርግ-ሊፐ (ጀርመን) | የሻውምቡርግ-ሊፐ ወንጌላዊ ቤተክርስቲያን | ሉተራን | 1910 |
ስኮትላንድ | የስኮትላንድ ቤተክርስቲያን | ፕሬስቢቲሪያን | አልተነቀለም |
ሰርቢያ | የሰርቢያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን | ምሥራቅ ኦርቶዶክስ | 1935 |
እስፓንያ | ሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን | ካቶሊክ | 1970 |
ስዊድን | የስዊድን ቤተክርስቲያን | ሉተራን | ጥር 1992 |
ቱርክ | እስልምና | 1920 | |
ቫልደክ (ጀርመን) | የሄሰ-ካሰልና የቫልደክ ወንጌላዊ ቤተክርስቲያን | ሉተራን | 1910 |
ዌልስ | የእንግሊዝ ቤተክርስቲያን | አንግሊካን | 1910 |
ቩርተምበርግ (ጀርመን) | የቩርተምበርግ ወንጌላዊ ቤተክርስቲያን | ሉተራን | 1910 |
^1: በ1959 ዓ.ም. የአልባኒያ መንግስት በይፋ ከሃዲነት «የመንግስት ሃይማኖት» አደረገና ሃይማኖቶች ሁሉ ከለከለ። ይህ ሁኔታ እስከ 1983 ዓ.ም. ድረስ ቆየ።
^2: የፊንላንድ ብሔራዊ ቤተክርስቲያን እስከ 1801 ዓ.ም. ድረስ የስዊድን ቤተክርስቲያን ነበረ። ከ1801 እስከ 1909 ዓ.ም. ድረስ ፊንላንድ የሩስያ ቅኝ አገር ስትሆን የተለየ የፊንላንድ ወንጌላዊ ሉተራን ቤተክርስቲያን በሩሲያ መንግስት በፊንላንድ ተመሰረተ። በ1911 ዓ.ም. ሕገ መንግሥት መሠረት ከፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጋር የጋርዮሽ ብሔራዊ ቤተክርስቲያን ነው።
^3: በፈረንሳይ ውስጥ በ1793 ዓ.ም. ስምምነት መሠረት የሮማ ካቶሊክ፣ የካልቪናዊ፣ የሉተራንም ቤተክርስቲያኖች እንዲሁም አይሁድና ሁሉ በመንግሥት የተደገፉ ሆኑ። በ1897 ዓ.ም. መንግሥት ከሃይማኖት ግን ተለየ።
^4: በሀንጋሪ የ1840 ሕገ መንግሥት መሠረት አምስት የጋርዮሽ አብያተ ክርስቲያናት ተመሰረቱ፤ እነሱም የሮማ ካቶሊክ፣ የካልቪናዊ፣ የሉተራን፣ የምስራቅ ኦርቶዶክስና የዩኒታሪያን ቤተክርስቲያኖች ናቸው። በ1887 ዓ.ም. አይሁድና ስድስተኛ የተምሰረተ እምነት ሆነ። በ1940 ዓ.ም. ግን የሀንጋሪ መንግሥት ሃይማኖቶቹን ሁሉ መለየት ተወ።